በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ት/ፅ/ቤት የምዕራፍ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት
በ2007 የተመሰረተ ት/ቤት ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በውስጡ ከ1100 በላይ ተማሪዎች በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ ት/ት መርሀ ግብር
እየተማሩ ይገኛሉ፡፡ በውስጡ አንድ የመማሪያ እና የቢሮ አገልግሎት ክፍሎችን የያዘ ህንፃ እና አንድ የተማሪዎች መመገቢያ አዳራሽ
ያለው ሲሆን መገኛውም በአዲስ አበባ ከተማ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ
10 አስተዳደር ሲሆን ልዩ ቦታው ከሸጎሌ አንበሳ ጋራዥ ጀርባ ነው፡፡